
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 18/2015 NBC Ethiopia- የጉምሩክ ኮሚሽን ከሐምሌ 7 እስከ 13 ቀን 2015 ባደረገው ክትትል 187 ሚሊዮን የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎችና ከ201 ሚሊዮን ብር በላይ የወጪ በድምሩ ከ389 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡ የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋዉሩ የተገኙ10 ግለሰቦች እና10 ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡

በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበ ሲሆን በዚህም በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ብቻ ከ176 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ ሀገር ገንዘቦችና አደንዛዥ እጾች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ የተያዙ ናቸው።
YouTube – https://www.youtube.com/@NBCETHIOPIA
TikTok – https://www.tiktok.com/@nbcethiopia
Facebook -https://www.facebook.com/ethiopiannbc