በአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19/2015፣ NBC ETHIOPIA-የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፤ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔውን በባሕርዳር ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡

ምክር ቤቱ ለአንድ ቀን በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ በክልሉ ወቅታዊ የሰላምና ደኅንነት ጉዳይ ላይ እደሚወያይ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ጉባዔው ከላይ በተገለጸው አጀንዳ ላይ ከተወያያ በኋላም ችግሮች በዘላቂነት ስለሚፈቱበት ሁኔታ የቀጣይ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል፡፡በተጨማሪም ምክር ቤቱ ሹመቶችን እንደሚሰጥ ነው የተገለጸው፡፡
YouTube – https://www.youtube.com/@NBCETHIOPIA
TikTok – https://www.tiktok.com/@nbcethiopia
Facebook -https://www.facebook.com/ethiopiannbc