
አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 11/2015፣ NBC ETHIOPIA-አሜሪካ የባክቴሪያ እና ቫይረሶችን ተፈጥሯዊ ይዘት በመቀየር አዲስ ወረርሽኝ እያዘጋቸች መሆኗን ሩስያ ስጋቷን ገልፃለች ።
ዋሽንግተን በተለያዩ የዓለማችን ሀገራት የተከሰቱ በሽታዎችን ናሙና በመውሰድ እና በቤተ ሙከራ ተፈጥሯዊ ስሪታቸውን በመቀየር ላይ ትገኛለች እየተባለ ነው ። የሩሲያ ጨረር፣ ኬሚካል እና ስነ ህይወታዊ መከላከል ወታደራዊ አዛዥ የሆኑት ኢጎር ኪሪሎቭ እንዳሉት አሜሪካ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በጣሰ መልኩ ምርምር እያደረገች ነው ሲሉ ከሰዋል።
ሀላፊው እንደሚሉት አሜሪካ የቤተ ሙከራ ሰራሽ ቫይረሶችን እንደ ጦር መሳሪያ ትጠቀምባቸዋለች ። በዓለማችን በየጊዜው በሚከሰቱ ወረርሽኞች በርካታ የአሜሪካ ኩባንያዎች ክትባት እና መድሀኒቶችን በማምረት ዋነኛ ገንዘብ ሰብሳቢዎች እንደነበሩ ህላፊው ገልጸዋል።
ፋና ክንፈ
YouTube – https://www.youtube.com/@NBCETHIOPIA
TikTok – https://www.tiktok.com/@nbcethiopia
Facebook -https://www.facebook.com/ethiopiannbc